Tuesday, 4 February 2020

New Counsultancy Duty

Empowering Marginal Economic Actors to Engage in Policy Reform From the Bottom-Up (EMEA)

Engaged in a consultancy duty with Pan African Chamber of Commerce and Industry specifically assuming the responsibility of overseeing the management and strategic intervention of the project activity.

EMEA is a project under implantation by a consortium member that include
1. Pan African Chamber of Commerce and Industry
2. Initiative Africa
3. Center for International Private Enterprise


Tuesday, 9 July 2019

ከስልጠን ጀርባ የድብቅነት ስነልቡና አባዜ

ጌታቸው መላኩ (የሚዲያና ተግባቦት አማካሪ)
በ getachewmelaku@gmail.com ላይ ሊያገኙአቸው ይችላሉ፡፡

በትርክት ሰምተን ከፅሁፍ ሰነዶች አንብበን፣ ነገር ግን ልክ እንደኖርንበት ጊዜ የምናውቀው (ከጊዜው ቅርበት የተነሳ ይመስለኛል) የቀዳማዊ ሀይለስላሴ አገዛዝ በተለይ ከጣሊያን ሽንፈት በኋላ በአንፃራዊ ሁኔታ የተረጋጋ ነበር፡፡ ማሳያውም ለረጅም አመታት የዘለቀው የአገዛዙ ስልጣን ከሌለው አንፃር ረጅም መሆኑ ነው፡፡ ነገር ግን ንጉሱ አለም ሲቀየር፣ ሀገር ወደ ውጪ እየተመለከተ ሲለወጥ ምልክቱን እንኳ መመልከት አቅቷቸው፣ እኛ በአለም ቢያንስ በግርማቸው የሚፈሩና የሚከበሩ ንጉስ እንደሰማነው በወታደሮች በትራስ ታፍነው ተገደሉ፡፡ ቀዳማዊ ሀይለስላሴ ከስደት መልስ ሀገሪቱን ለማረጋጋት የሄዱበት መንገድ እጅግ አስተዋይ ያስባላቸው ነበር፡፡ ሀገሪቱ ከ1933 ዓ.ም በኋላ በአርበኛ፣ በስደተኛና በባንዳ ተከፋፍላ ለዘላቂ የስልጣን መደላድሉ አስጊ ጊዜ ላይ ነበረች፡፡ እንግሊዞቹ ሳይቀሩ ላራሳቸውም ይሁን ለሌላ ምክንያት ራስ አበበን የመሰሉ አርበኞችን ስልጣን እንዲዙ ቢያበረታቱም ይህንን ጊዜ ለማለፍ ንጉሱ ያለፉበት መንገድ አስገራሚ ቢሆንም ይህ ብልሀታቸው በተለይ አስተዋነታቸው በስተርጅና የት ገባ የሚሉም አሉ፡፡ ድብቅ አባዜ ይሆን ይሆን?
የደርግ ወታደራዊ ስብስብ አብዮቱን ጠልፎ ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያን የተማሪዎችና የሌሎች አብዮተኞችን ትግል መስመር አሳተው፡፡ በሁለት አዋጆች/ደንቦች መሬትን ላረሹ እንዲሁም "ትርፍ" የከተማ ቤትና መሬት ለመንግስት ብሎ አብዮተኛውን በእጅጉ ጥያቄና ምክንያት አሳጣው፡፡ ይባስ ብሎ ዴሞክራሲያዊ መብትን ለመደፍጠጥ መሞከሩ የፈጠረው በተለይ በህቡዕ ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር የፈጠረው መላተም ብዙዎች ህይወታቸውን የገበሩበትን ክፉ አጋጣሚ ፈጠረ፡፡ አሁንም በደርግ ወታደራዊ ቡድንም ይሁን በህቡዕ በሚንቀሳቀሱት አካላት ውስጥ የራሳቸውም ሆነ ኢትዮጵያዊ የሆነ የድብቅነት ስነልቡና ተጠቂዎች ያደረጋቸው ስሪት እንዳለ ይሰማኛል፡፡ በተጨማሪም የአሸናፊና ተሸናፊው ስልቡና አሁንም ድረስ እያማሰነን ይገኛል፡፡
ኢህአዴግና ሻቢያ ለአመታት የዘለቀ "ከቀኝ ገዢ" ስርአት የመላቀቅና  የራስን ክልል "ነፃ የማውጣት" ጦርነት እንዲሁ በድብቅነት ስነልቡና በተጠናወተው ምክንያት ተሸፍነው ባደረጉት ተጋድሎ አንዷ ሀገር ሁለት ሆነች፡፡ ለዘመናት በድብቅ አጀንዳ ተታሎ ነፃ የመውጣት እንቅስቃሴውን የደገፈው ህብረተሰብም የሌላ ዙር "ቀኝ ገዢ" ሰለባ  ሆኗል ብለው የሚከራከሩ ብዙሀን ናቸው፡፡ የማይታበለው ሀቅ ግን ብዙዎች የስኳር ነገር አልሆን በሏቸው የድብቅ ነፃ አውጪነት ካባቸው እስኪገለጥ ድረስ ሞሰኑ፣ ነቀዙ፣ ተበላሹ ድመት ብትመነኩስም አስተረተባቸው፡፡ ይህም የድብቅ ስነልቡናቸው መገለጫ ሆኖ ወጣ፡፡ ከኢህአዴግ ውስጥ ጊዜው እድል የፈጠረላቸው ከወስጥ ገፍተው ስልጣን ሲይዙ ከውጪ የነበረውን ግፊት በመመልከት የጠለፋ ያህል የጥያቄው ወራሽ ሆነው ብቅ ያሉት እነዚህ አካላት የድብቅ ስነልቦናው ችግር ተጠቂ ይሁኑ አይሁኑ ጊዜ የሚፈታው ጉደይ ነው፡፡
የሚገርመው ነገር ይህ የድብቅነት ስነልቡና ችግር በመንግስትነት ባሕርይ ሁሉንም ሲጎዳ ጎልቶ ይታይ እንጂ አጋጣሚዎች እያሳየን ያሉት ይህ የድብቅነት ስነልቡና በግለሰብ፣ በቤተሰብ፣ በድርጅትና በማህበረሰብ ደረጃ የሚንፀባረቅ ችግር መሆኑን ነው፡፡ ከጓደኝነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፣ ከትዳርና ቤተሰብ ምስረት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፣ ከድርጅት ባልደረብነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፣ ከማህበረሰብ አባልነት እንዲሁም ወኪልነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፡፡ ከአነቃቂ ንግግር አቅራቢነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነ ልቡና፣ ከስራ ፈጠራ ስኬት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፣ ከበጎ አድራጎት ተግባር ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፣ ከፓርቲ አባልነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፡፡ የድብቅ ስነልቡናው ዝርዝር በየፈርጁ ማለቂያ ሳይኖረው ሊቀጥል ይችላል፡፡ ከተቃዋሚነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፣ ከደጋፊነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፣ ከፓርቲ መሪነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና፣ ከሀገር መሪነት ጀርባ ሌላ ድብቅ ስነልቡና ዝርዝር ያደክማል፡፡
ለዚህ ጉዳዬ አስረጅ እንዲሆነኝ እስቲ እንድ ምሳሌ ላንሳ፡፡ የሰሞኑ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ጉዳይ እጅግ የሚገርም ነው፡፡ በየማህበራዊ ሚዲው የሚገልፀውና የሚሰራጨው መልእክት፣ ኢሳት ባለደረቦቹን በአመለካከታቸው ምክንያት የማግለል ስራ እየሰራ እንደሆነ ሲሆን፤ ድርጅቱ ያወጣው ግልፅነት የጎደለው መግለጫ (ለአላማ እንደሆነ በድንብ ስለሚያስታውቅ ኢሳቶች ቢያስቡበት መልካም ነው) ደግሞ የሚያትተው የለውጥ ሂደት እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሆነ ነው፡፡
ኢሳት በሀገሪቱ ለመጣው ለውጥ እንደ ብዙሀን መገናኛ ጣቢያ ዋነኛ ድርሻ እንዳለው የማይታበል ነው፡፡ ብዙዎች ግን ሙያዊ ስነምግባርን በተለመከተ በኢሳት ላይ ጥያቄ አላቸው፡፡ በጊዜው ኢሳት የነፃ አውጪ አይነት እንቅስቃሴ በስሜት ያደርግ ስለነበር ይመስለኛል፡፡  የዚህ አይነቱ የብዙሀን መገናኛ ስነምግባር የማይደገፈው በምክያትና በማስረጃ ከሚያምን ተከታይ ይልቅ ስሜቱን የሚከተል ተከታታይ መፍጠሩ ነው፡፡ የሚገርመው ይህ ተከታታይ ሁኔታዎች የተቀየሩ ዕለት በራሱ በጣቢያው ላይ መነሳቱ የማይቀር ነበር፣ እንሆ ሆነ፡፡
የለውጡን መምጣት ተከትሎ በኢሳት ውስጥ በተለይ በተፅእኖ ፈጣሪነታቸው የሚታወቁት ግለሰቦች የለውጡ ግልፅ ደጋፊ ሆነው መምጣታቸው ባያስገርምም፣ በኢሳት ውስጥ ለሀሳብ ልዩነት የሚሰጠው ቦታና ግምት እንደተወራውና እንደተዘመረው እንዳልነበር የሚያሳዩ ነገሮች ከለውጡ መምጣት ማግስት ጀምሮ መከሰት ጀምረው ነበር፡፡ ይህም አብዛኛውን ተመልካችና አድማጭ አሁን ከአንድ ዋንጫ መጠጣት ሊቀር ነው፤ የሀሳብ ፍትጊያ የሚያመጣውን ልዕልና ልናይ ነው፤ ያለው አድማጭ ተመልካች በርካታ ነበር፡፡ በእርግጥ በኢሳት ላይ የነበረውን የቆየ የብዙሀን መገናኛ ጣቢያነት ሚናን ያኮሰሱና የነፃ አውጪ ግንባርነት ሚናን ያላበሱ የቀን ተቀን አሰራሮች በብዙዎች ዘንድ አልተዘነጉም፡፡ እንዲሻሻሉ ለማገዝ ያሰበና መሳተፍ የቆረጠ ሰው ቢያንስ በእኔ ዙሪያ እንደነበር አውቃለሁ፡፡  
ነገር ግን አሁን ሁኔታዎች የሚያሳዩት እንደ ሌላው ሁሉ ኢሳትም የድብቅ ስነልቡና ችግር ተጠቂ የሆነ ጣቢያ መሆኑን ነው፡፡ በእርግጥ ከአሀገራቸው ተሰደው የነበሩ ግለሰቦች ወደ አገራቸው የመመለስ እድል ማግኘታቸው አስደሳች ነው፣ ለእነሱም፣ ለቤተሰባቸውም እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዳቸው፡፡  ከጥቂት ቀናት በፊት ታማኝ በየነን አንድ ሆቴል ውስጥ በአካል ስመለከተው እኔንም ለየት ያለ ስሜት እንደተሰማኝ ልደብቅ አልፈልግም ፡፡ ከሀገር ከወገን በተለይ የመለየት ሰሜቱ ለኢትዮጵያዊ ካልደረሰብት በቀር ለመረዳት ስለሚከብድ ባልፈርድም  ለማስረዳት ግን ከባድ ጉዳይ የሚሆንብኝ ይመስለኛል፡፡ ለጥቂጥ አመታት ለትምሀርት እንኳ ሀገርን ሲለዩ የሚሰማው ስሜት ባያስቸግረኝም ጎሻሽሞኛል፡፡ ነገር ግን የኢሳት ባልደረቦች በተለይ "ተፅዕኖ ፈጣሪ" ሰዎች ድብቅ አላማ ወደ ሀገር ቤት የመግቢያ እድል ለማግኝት ወይስ እውነተኛ የሰላምና የዴሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት የሚደረግ ጥረት ድጋፍ፡፡
የድብቅ ስነልቡና መነሻው ምንም ይሁን ምን ችግሩ ግን ግለፅ ነው፡፡ በመጀመሪያ ግለሰቦች ባለባቸው የድብቅነት ስነልቡና ምክንያት የረጋና የተመቻቸ ህይወት እንዲሁም ውጤታማነት ሲርቃቸው፤ በአንድ አጋጣሚ የሰሩትን መልካም ስራ በሌላ ጊዜ በተቃራኒው እያጠፉ የመኖር አባዜ ውስጥ ይከታቸዋል፡፡ ድርጅቶችም እንደዚሁ ብዙ ድብቅ ስነልቡና ባላቸው ግለሰቦች ተወጥረው የአመፃና የተንኮል አውድማ ሲሆኑ፣ የማደግና የመለወጥ እድላቸው መክኖ ለሌሎች ውድቅና ክሽፈት ምክንያትም ሲሆኑ ይስተዋላል፡፡ ድብቅ ስነልቡና በሀገር ደረጃ ያስከፈለንን ዋጋ ስንመለከተው ከበሽታነቱ አልፎ ሞተን ወደ መቃብር ካልወረድን የማይተወን ክፉ ደዌ እንደሆነብን የተረዳን አይመስለኝም፡፡
በተለይ የወላጅ፣ የአስተዳዳሪ፣ የአመራርና የእናትነት/የአባትነት ሃላፊነት ያለባቸው ሰዎች የድብቅነት ስነልቡናው ችግር ተጠቂነት እየጨመረ መምጣቱ ወላጅ አልባ፣ አስተዳደሪ የማይበረክትለት፣ መሪ ያጣ፣ እጓለማውታን አድርጎን እነሆ ለዘመናት ዘለቀ፡፡ ለመፍትሄው ማን ምን ያስብ ሆን? የድብቅነት ስነልቡና በእኛ ሀገር በሰፊው መገለጫ የሆነው "የጠላቴ ጠላት ለእኔ ወዳጄ ነው" በመሆኑም፤ ጠላቱ የጠፋ ዕለት ወዳጅነትን የሚያዘልቅ አላማም ይሁን ተነሳሽነት ሲጠፋ ይስተዋላል፡፡ "እውቀት የጎደለው ይጎዳል አስተወሎት የጎደለው ደግሞ እጅግ ይጎዳል" ነውና በጠላቴ ጠላት አላማ መስተጋብር የፈጠረ ሁሉ ጠላቱ ሲጠፋ ወይም ሲዳከም አስተውሎ የጎደለው ስለሆነ ከጠላቱ በላይ መበታተኑ መድከሙና መውደቁ ያስገርማል፡፡ ድብው ስነልቡናና አባዜው ማለት ይህ ነው፡፡
ከሙያና ከመስሪያ ቤት ምርጫ ጀርባ ድብቅ ስነልቡና፣ የፖለቲካ ፓርቲ ከማደረጃት ጀርባ ድብቅ ስነልቡና፣ የብዙሀን መገናኛ ድርጅት ከማደራጀት ጀርባ ድብቅ ስነልቡና፣ የበጎ ድራጎት ድርጅት ከማቋቋም ጀርባ ድብቅ ስነልቡና፣ ከሰፈር ልማት አስተባበሪነት ጀርባ ድብቅ ስነልቡና እንዲሁም ሲብስ ጓደኝነት ከመመስረት ጀርባ ድብቅ ስነልቡና ወዘተ... ኢትዮጵያዊነታችንን አውርደውታል፡፡
መድረሻችን የት ይሆን?
ድብቅ ስልቡና የግልፅ ስነልቡና ተቃራኒ ነው፡፡ በግልፅ ንልቡና ሰዎች የምንሻውን እንመኛለን፡፡ እርሱን ለማግኘት እንጥራለን፡፡ ሌሎች ፍለጎታችንንና ጥረታችንን ተመልክተው ሊረዱን ባይችሉ እንኳ ምንገዳችን ላይ በመቆም ደንቃራ ከመሆን ይታቀባሉ፡፡ በዚህ የቀጠለና ያደገ የግልፅነት ስነልቡና ግንዛቤ ባይኖ መማርን፣ ቢሳሳቱ ማረምን፣ ቢበድሉ ይቅርታ መጠየቅን ስለሚያስተምርና በውስጣችን ስለሚያዳብር መለወጥ እንችላለን፡፡ በመሆኑም ግለሰባዊ እድላችን፣ እንደሀገር ፅዋ ተርታችን በተጠናወተን የድብቅ የስነልቡነ ችግር  እንዲቀረፍ ብንተጋ፡፡ ግላዊ አስተሳሰብና አመለካከት ክቡር ሆኖ ሳለ ለድብቅ ስነልቡና የሚዳርገን ችግር በትውልድ ላይ ብንሰራ፡፡ 

አሮጌ ሀሳብን አዲስ ልብስ ማልበስ እንዳይሆን


አሮጌ ሀሳብን አዲስ ልብስ ማልበስ እንዳይሆን
ጌታቸው መላኩ (የሚዲና ተግባቦት አማካሪ)                        

ሰሞኑን አንድ ለውጥ ተኮር በተለይ ድርጅታዊ ለውጥ ተኮር ጉዳይ ላይ ሀሳቤን እንዳካፍ በአንድ ድርጅት ከፍተኛ አመራር ተጋብዤ ነበር፡፡ ግብዣው ሳይገርመኝ አይቀርም፡፡ ምን ትልቅ ነገር ሰርቼ ነው የእኔን ሀሳብ ለመጋራት የተጋበዝኩት የሚል ሀሳብም ውስጤ ይብላላ ጀመር፡፡ ወደ አእምሮዬ ጓዳ በመዝለቅ የተለየ ነገር ፍለጋ ስባክንም ሰነበትኩ፡፡ ወደ መረጃዎቼና መፃህፍቶቼም ማስቀመጫ አልፌ ልዩ ነገር ፍለጋ ቀናትን አጥፈቼ ነበር፡፡ ያላስቀመጡትን ፍለጋ ማለት ይህ ነው!!!
ለማንኛውም ጠሪ አክባሪ ነውና ያለችኝን ለማካፈል ወስኜ ለማዘጋጀት ሳስብ ሁለት አጋጣሚዎች እንደ መልካም አጋጣሚ ተከሰቱልኝ፡፡ አንደኛው የማህበራዊ ብዙሃን መገናኛ ላይ ያየሁት በድርጅቶች አመራር መካከል የትውልድ ልዩነት ሲኖር መስተጋብሩ ምን ይመስላል? ልዩነቱ አሳሳቢስ ከሆነ ምን ማድረግ ይበጃል? የሚል ጉዳይ ነበር፡፡ በዚህም የተለያዩ ታዋቂ የድርጅት ዘላቂ አመራር ባለሙያዎች ያወሱትን ጉዳይ ሳሰላስል ቆየሁ፡፡ በዚያ ላይም ተመርኩዤ ሀሳቤን በማደራጀት ላይ እንዳለሁ ሁለተኛው ገጠመኝ ተከሰተ፡፡
ሁለተኛው ገጠመኝ በኢትዮጵያችን ያሉ በተለይም በዋናነት ከውጪ ሀገር በስደት ቆይተው የዶ/ር አብይ ቡድን ወደ ስልጣን መምጣቱን ተከትሎ በተፈጠረው ምቹ አጋጣሚ የገቡት የፖለቲካ ፓርቲዎች መክሰማቸውን ሰማሁ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ አዲስ ፓርቲ ለማቋቋም ስብሰባዎች እየተካሄዱ መሆናቸውን ተመለከትኩ እንዳዶቹንም ለመታደም ሞከርኩ፡፡ ነገር ግን አሁንም የታዘብኩት ነገር ቢኖር በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ አሁንም ፊትአውራሪዎቹ ላለፉት ሰላሳ አመታት ከዚያም በላይ የምናውቃቸው ፊቶች ሆነው ማግኘቴ ነው፡፡ በሰለጠነው አለም የተለመደ እንዲያውም ተቀባይነት ያለው ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ የፕሬዚደንት ኦባማ ጊዜ ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ጆ ባይደን አሁን ደግሞ ለፕሬዚደንትነት ለመወዳደር እየተዘጋጁ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ ይህንን ውሳኔታቸውን ተከትሎ በተለያዩ አካላት አይመጥኑም፣ በተለይ ፆታዊ መስተጋብራቸው ስርዓት ይጎድለዋል ያሉ ከሳሾች ቢነሱባቸውን እሳቸው ግን በሀሳባቸው እንደሚገፉበት አስረግጠዋል፡፡
በእኛ ሀገር ግን  ባለፉት አርባ እስከ ስልሳ አመታት ውስጥ በፖለቲካ ትግል ስም የምነዋቃቸው ግለሰቦች አሁንም የአዲሱ ፖለቲካ ምህዳር ዋነኛ ተዋናይ ሆነው መጥተዋል፡፡ ልምድ እጅግ ትልቅ አበርክቶ እንዳለው የማይስተባበል ቢሆንም ከላይ ያነሳሁት የትውልድና ዘመን ልዩነት እነዚህን ግለሰቦች ውጤታማ ያደርጋቸው ይሆን? የሚልም ስጋት ጭሮብኛል፡፡ ከላይ ወደተነሳሁበት ጉዳይ ልመለስና ንፅፅር ለማድረግ በመሞከር እነዚህ ዘመናትን የተሻገሩ አንጋፋ ፖለቲከኞች በአዲሶቹ ፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ ሊገጥማቸው የሚችለውን ተግዳሮቶች ለማመላከት ልሞክር፡፡
የአመራር ተመክሮ
እነዚህ አዲስ ፓርቲዎችን በነባር መሪዎች ጠርናፊነት ወደ ሜዳው ከገቡ ሊከሰቱ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ከመልካም አጋጣሚዎቻቸው መሳ ለመሳ ለማንሳት ልሞክር፡፡ ተግዳሮታቸው የትየለሌ ናቸው ብለው የሚከራከሩ ብዙዎች አሮጌን ሀሳብ አዲስ ልብ አልብሶ ማምጣት ሲሉት፤ የነባር ፖለቲከኞችን ተሳትፎ የሚደግፉት አካላት ደግሞ "ወይን የሚጥመው ሲቆይ ነው" በማለት ይከራከራሉ፡፡ ለማንኛውም ከሳይንሳዊ መነሻ ጉዳዩን ማየት ለግንዛቤም ለገንቢ ትችትም ስለሚጣቅም ከዚያ እንፃር ለማየት ልሞክር፡፡
በመጀመሪ ደረጃ የትውልድ ልዩነት በሚንፀባረቅበት ተቋም ውስጥ የሚንፀባረቁጽ ችግሮች መነሻቸ የልምድና ተመክሮ ጉዳይ ነው፡፡ ቀዳሚው ትውልድ በአብዛኛው ኑባሬያዊና ተዋረድን የጠበቀ አመራርና አሰራር ለማስፈን እንደሚጥር የእስትራቴጂ ሊቁ ዶ/ር ፒተር ሴነጄ ሲናገሩ፤ የኋለኛው ትውልድ ደግሞ በአመራር ፍልስፍናው ከፈጣንና ልዩነትን የሚፈጥሩ እርምጃዎች ላይ ያተኩራል፡፡ ይህም በዶ/ር ፒተር አገላለፅ  (Traditional/Hierarchical leadership Vs. Dynamic and Breakthrough leadership) ይባላል፡፡
እንደ ዶ/ር ፒተር አገላለፅ በጣም ጥቂት መሪዎች ዘመን ተሻጋር የሚባለውን ሁለቱን እሳቤዎች የማቀናጀትና የመጠቀም አቅም ሲኖራቸው ብዙ መሪዎች ግን ሲቸገሩ ይስተዋላል፡፡ በሆኑም በነባር አመራሮች የሚመሰረቱት አዳዲስ ፓርቲዎች የሁለቱን ዘመን ጠቀስ እሳቤና ልነቶች የማቻቻል አቅምና ችሎታቸው መፈተኛ የቤት ስራዎቻቸው ይሆናሉ፡፡
ሁለተኛው የቀዳሚው ትውልድ በአዲስ ትውልድ ፓርቲዎች ላይ የመሳተፍ ተግዳሮት የእሳቤ አድማስ (imagination) ላይ ያለውን ልዩነት በማንፀባረቅ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ የእሳቤ አድማስ (imagination) የነገሮችን ሁለንተናዊ ቁመና (ስፋት፣ ጥልቀት፣ አስቸኳይነት፣ ምስጢራዊነት፣ ጊዜ ተሻጋሪነትና) የመሳሰሉትን ነገሮች ያካተተ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ የእሳቤ አድማስ ልዩነት የጉዳዮችን ትርጉም በግልፅ በትውልዱ መካከል ይፈጥራል፡፡ ይህም ለመግባባትና ልዩነትን ለማቻቻል የሚደረጉ ጥረቶች ጥግ ድረስ የመጓዝ ፈቃደኝነት ኖሮ መልካም መግባባት ቢኖርም፤ ሁለግዜ የሚሳካ ጉዳይ ሊሆን ስለማይችል ልዩነቶች ከባድ ሆነው በሚመጡበት ጊዜ ድርጅታዊ አቋም ሊፈተሽ ይችላል፡፡
ለውጥን በበጎ የመመልከትና የመሻት ጉዳይ (adaptation to change)
ለውጥ የማይቀር ጉዳይ እንደሆነ በርካታ ምሁራን የሚስማሙበት ጉዳየ ሆኖ ሳለ፣ የማትቀረውን ለውጥ መፍራት ወይም ለመከላከል መሞከርን ነባራዊ ተቃርኖ (Existing paradox) ይሉታል፡፡ ምሁራን የመሪዎችን ስራ መፈተሻ መሰንክልም ይኸው ለውጥ እንደማይቀር እየታወቀ የሚፈተር መከላከል ነው፡፡ ምሁራን በለውጥ ጊዜ የሚተሉትን የመከላከል ግባራትን የማክሸፊያ መንገዶች ብለው ካስቀመጧቸው ስልቶች መካከል የለውጥ አካላትንና ተዋንያንን የስሜት ደረጃ በመከታተል ሃለፊነትን መወጣት ሚለው ቀዳሚ ቦታ ይሰጠዋል፡፡ በመሆኑም ተዋንያንን የመምራት ጉዳይ እጅግ አስፈላጊና አስትራቴጂዊ ጉዳይ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህም ለውጥን በበጎ ለመመልከት የመሻት ሁኔታን ይፈጥራል፡፡
አሮጌ ሀሳብን በአዲስ ልብስ የመምጣቱ ፍርሀት በእኛ
ከግማሽ ደርዘን በላይ ፓርቲዎች ከስመን (እስካሁን ህጋዊ ስርአቱ ተጥሷል የሚለው ጭቅጭቅ ባይቋረጥም) አዲስ ህብረ ብሄራዊ ፓርቲ አቋቁመናል ካሉን ሳምንታት ተቆጥረዋል፡፡ በዚህም ጊዜ አንደ ሁለጊዘው በርካቶች በተስፋ ትቂቶች ደግሞ በጥርጣሬ ከዚያም ያነሱት ደግሞ በፍርሀት ጊዜ የሚያመጣውን እየጠበቁ ይገኛሉ፡፡ ተስፈኞቹ በአብዛኛው ትንታኔ ሳይኖራቸውና ሳያሻቸው "መልካሙን ነገር የሚያመጣው ፈጣሪ ነው" ብለው የሚያምኑ እንደሆነ ያደረኩት ጥቂት ግምገማ አሳይቶኛል፡፡ ቀሪዎቹ በአዲሱ ፓርቲ መሪዎች ልምድና ተመክሮ ሚተማመኑ ይመስላሉ፡፡  በጥርጣሬ ሁኔታውን የመከታተሉት ደግሞ የሀገራችን ፖለቲካ ከልምድ ከሚገኝ ብስለት ይልቅ ደራሽ ስሜት የሚነዳው ሆኖ ስላገኙት መጠርጠርን መርጠዉ ሚተባበቁ ይመስላሉ፡፡ እነዚህ አካላት ሁኔታዎች ባይሳኩ ማንንም ምክንያት አድርገው ማማረር የሚፈልጉ አይመስሉም፡፡ ይልቁንም በሂደት ሌላ አማራጭና ችግር መፍቻ ዘዴን የሚስቡ ይመስላሉ፡፡ "ፈሪዎቹ" የሰለባዎች ስነልቡና ምርኮኛ የሆኑ ይመስላል፡፡ በእነዚህ ግለሰቦች ላይ ሀሳብ የመስተት ማንም የሞራል የበላይነት ያለው አይመስለኝም፡፡ ይልቁን ጠባሳቸው ለሌሎች ትምህርት ሆኖ እንዲታይ መፈለግ አዝማሚያ ያሳያሉ፡፡
በመጨረሻም የለውጡ ሂዳት በግለሰብ አመራር ላይ ብቻ የሚንጠለጠል እንዳልሆነ ይታወቃል፡፡ ነገር የመሪዎች ግንዛቤና አቋም ደግሚ አይነተኛ ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም የአዲሱ ፓርቲ መሪ ነባር ታጋዮች ዘመናቸውን መዋጀት ዋነኛ ስራቸው መሆኑ የሰማኛል፡፡ መፅፉም ዘመኑን ዋጁ ይለናልና፣ እዩት መርምሩት አስፈላጊውን ጉዳይ ለዩና ስሩበት ማለት የመስለኛል፡፡
ልቡና ለመሪዎቻችን ዘመናቸውን እንዲዋጁ!!!

Thursday, 2 May 2019

Jermy HUNT,
UK's Foreign Secretary is attending the 2019 World Press Freedom Day.

UK to provide 15.5 million pounds for supporting the 2020/2012EC elextion in Ethiopia.

Thursday, 6 September 2018


የዜና ትንታኔ ዝግጅት መመሪያ



መግቢያ

ለዜና አዲስ ህይወት የሚሰጥ ትንታኔ ነው፡፡ የዜን ትንታኔ ለመስራት በደንብ መዘጋጀት ይጠይቃል፡፡ በመጀመሪያ ራስን በሚነሳው ጉዳይ ላይ ልዩና ጠቃሚ የመረጃ ምንጭ አድርጎ ማሰብ ይጠይቃል፡፡ በዚህ ዝግጅት ውስጥ የሚሰራውን ትንታኔ ስራ ሳቢ ከማድረግ ባሻገር ለቀጣይ ስራ የሚሆን የመጣጥፍ ሀሳብ ምንጭ ሆኖ ሊያገለግልም ይችላል፡፡



በዜና ስራ ላይ ያለው ዋናው ትኩረት ዜናው ጊዜ አልፎበት ተገላጊነቱን እንዳያጣ መስራት ነው፡፡ በዜና ትንታኔ ቢሰራ ግን ግቡ የተዘገበው ዜና ለወደፊት ጭምር ጠቀሜታው እንዲዘልቅ ለማድረግ ነው፡፡ ለዚህም አንደኛው መንገድ ትኩረታችንን ወደፊት በሚሆነው ነገር ላይ ትንታኔያችንን ስንሰራ ነው፡፡ ሌላው በትንታኔያችን ውስጥ ያለፈውን ጊዜ አካተን መመልከት መቻልን ያካትታል፡፡

ስኬታማ የዜና ትንታኔ ስራ የሚከተሉትን ደረጃዎች የጠበቀ አሰራር ይከተላል፡፡

1.   ርዕስ መምረጥ - በመረጥነው ርዕስ/ትኩረት ዙሪያ ዜናዎችን በመለየት ማድመጥና መከታከል ከዚያም የተለያዩ ምንጮችን ማገላበጥ ሁልጊዜ አዲስ ነገር እንድናውቅ ይረዳናል፡፡ ለትንታኔ ስራችንም ትልቅ ግብአት ይሆነናል፡፡

2.   ታሪኩን መወጠን - የዘገባውን መቼት መለየት የመጀመሪያ ተግባር ይሆናል፡፡ ይህንን ክፍል በአጭሩ በማስቀመጥ የቀረውን ክፍል ለዋናው ጉዳይ በተለይ መያዝ ያስፈልጋል፡፡

3.   ትንተና መስጠት - በትንታኔያችን የምንሰራው ከላይ የመረጥነው የትኩረት ጉዳይ ከተለያየ እይታ የሚሰጠውን እንድምታና ምስል ለአድማጭ በመረጃ በማጣቀስ የማሳየት ስራ ነው፡፡ በዚህም ገለፃ በተነሳው ጉዳይ ላይ ብዙዎች የያዙትን ግንዛቤና እምነት እንዲቀይሩ ወይም አጠናክረው እንዲገፉበት ማስቻል አላማው ነው፡፡

4.   ትንበያን ማስቀመጥ - በጉዳዩ ላይ የወደፊት ክስተቶች ምን ሊሆኑ እንደሚችሉና ያላቸውን የተፅዕኖ ደረጃ ለማሳየት መሞከርን በዚህ ተግባር ትኩረት ልንሰጠው የገባል፡፡ ይህ ተግባር በመጠኑ የሰፋ ሙያዊ ግንዛቤ መያዝን ስለሚጠይቅ በሀላፊነት ስሜት ሊሰራ ይገባል፡፡ ይህም ክፍተት ተገቢውን መረጃዎች ከተለያዩ ምንጮች በመሰብሰብ ማደራጅንና ማዋሀድን ይጠይቃል፡፡

5.   ትንተናውን መጠቅለል - መነሻ የነበረውን የትኩረት ዘገባ እንደገና በማስታወስ ከሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ጋር ያለውን መስተጋብር ማሳየት በዚህ ደረጃ የሚተገበር ስራ ነው፡፡

ውጤታማ የዜና ትንታኔ ለመውጣት ስራውን የምንገመግምባቸው መስፈርቶች የሚከተሉት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

ሀ. ጠቀሜታ - ለትንነታኔ የተመረጠው ርዕሰ ጉዳይ ከአድማጭ አንፃር ጠቃሚ መሆኑን መለየት

ለ. የማይሞት - የማይሞት ይዘትን በማንሳት ለወደፊት አንባብያንና አድማጮች ፍላጎትን የሚያርፍበት እንዲሆን ማስቻል፡፡

ሐ. ከአድልዎ የፀዳ - ትንታኔው ወደ አንድ ወገን ያደላ መሆኑ ጎልቶ ተአማኒነትን እንዳያወርድ መጠንቀቅ፣ ጨለምተኝነትን ማስወገድ፣ የሞቱ ጉዳዮችን ማንሳትና ትፅዕኖኗቸው ከባድ የሆኑ ጉዳዮችን ሀላፊነት በጎደለው መልኩ መነካካት አግባብ አይደለም፡፡

መ. እውነት - መረጃ ይኑረን፡፡ በጊዜው ያሉ ጉዳዮች የአድማጮችን ትኩተር ይስባሉ፡፡ በመሆኑም እውነተኛ ነገርን በማንሳት ከአሉባልታ መራቅ ያሻል፡፡

ሠ. አሳዋቂ - ስድስቱን የ ‘ምን’ ጥያቄዎች በመመለስ ትንታኔው ሚዛኑን የጠበቀና የወደፊቱን አመላካች እንዲሆን መስራት ያስፈልጋል ፡፡ (ምን፣ ማን፣ መቼ፣ የት፣ ለምንና እንዴት)

ረ. ብቸኛ ዘገባ - ለአድማጮች ሙሉ በሙሉ ልዩ ይዘት በማቅረብ ብቸኛ የዘገባው ምንጭ ለመሆን ማሰብና መስራት የስፈልጋል፡፡

ሰ. ዋጋ ያለው - የትንታኔ ዘገባው ባንጠለጠለው ትርፍ ጉዳይ ሳይሆን በጥልቀት ባነሳው ዘገባ ዋጋ እንዳለው መረጋገጥና ማሳየት፡፡
እነዚህን መገምገሚያ መስፈርቶች በመጠቀም የዜና ትንታኔያችንን ልዩ፣ አስተማሪና ጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ እንችላለን፡፡ ትንታኔ በተደጋጋሚ በመስራት ልምድን በማዳበር ጉዳዮችን በጥልቀት ለማየት ከማስቻሉም ባሻገር በጥሩ ተነሳሽነትና የአእምሮ ዝግጅት ላይ ለመድረስ ያስችላል፡፡  
A Training on Security Report Writing was underway for S&S Property Administration and Security Service

Content

What is a report?

How security report is different?

What a report entails?

Characteristics of good report

Types of security reports

Writing a regular/Duty report

Writing an incident report

Writing a maintenance report

Important issues of security report

Writing a report

Completing a report

Tips to improve security report

Retaining records of reports  

Tuesday, 5 June 2018

የጋዜጠኛና ጋዜጠኝነት ተግዳሮቶች በአሁኑ ዘመን


የጋዜጠኛና ጋዜጠኝነት ተግዳሮቶች በአሁኑ ዘመን
ጌታቸው መላኩ
ግንቦት 23 2010
አዲስ አበባ

በዘመናችን ሰዎች ለቁጥር በሚያዳግቱ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ፡፡ አነዚህም ለሰዎች የቀን ተቀን ኑሮ ገቢ ከሚያስገኙት እስካ ሙያዊና ህይወታዊ ጥሪ ሆነው የሚከወኑትን ስራዎች ያካትታል፡፡ ነገር ግን  በሁሉም ዘርፍ ውጤታማነት ተዋናዩን ሁሉ የሚያስደስት ነው፡፡

አንዳንድ ስራዎችን ጊዜና ሁኔታዎች ይገድቧቸዋል፡፡ በዚህም የተነሳ አላማቸውን በብቃት ሲያሳኩ አይታዩም፡፡ ለምሳሌ የማምረቻ ፋብሪካዎች የስራ ሰዓት አዋጅ፣ የሀይል አቅርቦት የድርጅቶቹ የስራ ሰዓት ስምሪት አቅምና ሌሎችም ነገሮች የገድቧቸዋል፡፡ ለእነዚህ ገዳቢ ኩነቶች ምላሽ በመስጠት የ24 ሰዓት እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ጠቋማት እንዳሉ ያጤኗል፡፡
የሁሉም ተቋመት ግብ ቢያንስ በአላማ ደረጃ ግን አቅማቸውን አሟጣ በመጠቀም ውጤታማና ትርፋማ መሆን እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡
ተቋማት የሰዎች አስተሳሰብ መገለጫና ውጤት ናቸው፡፡ ከላይ የገለፅናቸው በተላያዩ ሁኔታዎች የተገደቡም ይሁኑ ለእነዚህ ሁኔታዎች ምላሽ ሰጥተው ሙሉ አቅማቸውን ለመጠቀም የሚታትሩ ተቋማት የመሪዎቻቸውና የሰራተኞቻቸው የአስተሳሰብ አይነትና ደረጃ መገለጫዎች ናቸው፡፡ በማናቸውም ሁኔታ ግን ስራን በውጤት መተርጎም በአስተሳሰብ ደረጃ የማንኛውም ተቋም ባልደረባ አላማና ፍለጎት ቢሆንም፤ ተግባራዊ መገለጫው ግን ግንዛቤ ደረጃውና በልምዱ ከሰዎች ሰዎች ይለያያል  አንዳንዴም ጭራሽ አይገጥምም፡፡
ባለንበት ዘመን ሰዎች ወደስራቸው ሲገቡ ባለፈው የስራ ቀን የጀመሩትን ዛሬ ለመቀጠልና የስራ ሰዓት እስኪገባደድ ጠብቀው ለመተግባር ከሆነ ችግሩ አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ ይመስለኛል፡፡ ማንኛውም ስራ የሚፈልገው የእውቀት የክህሎትና የአመለካካት ደራጃ የሚለያይ የማቀድና ውጤትን የማለም ተዘክሮ አለው፡፡ የውጤት ተኮር ስራ አመራር "በአጋጣሚ" ከቀየራቸው የጥበቃ ሰራተኞች ልምድ እንደተረዳሁት እምነታቸው የሚጠብቁት ንብረት በተሰማሩበት ቀንና ሰዓት አለመጉደሉን ማረጋገጥ ዋና ተግባራቸው ቢሆንም ንብረቱ ለስርቆት ሊዳረግ የሚችልበትን መንገድና አጋጣሚ ቀድሞ በመለየት አደጋን ቀድሞ ማስወገዱ ከተራ ሰራተኝነት የዘለለ ባለሙያ እንደሚያደርጋቸው አምነው ተቀይረዋል፡፡ በመሆኑም ስራ ከተራ የዕለት ከዕለት ተግባር ባለፈ ሙያዊ ተሰጥቶና አስተዋይነት ወደሚለካበት የአተገባበር ደረጃ  ካላደገ አሰልቺ፣ ውጤት አልባና በስተመጨረሻም ተጠያቂነትና ጉዳት ላይ የሚጥል ውጤት እንደሚመጣ እሙን ነው፡፡
እንዳንድ ስራ ዘርፎች ከሌሎች በተለየ እቅድ ሲሹ አንዳንዶች ደግሞ ልዩና ተገማች ባለሆኑ አጋጣሚዎችና ሁነቶች የተከበቡ በመሆኑ ለተግባራዊነታቸውና ውጤታቸው የተለየ ትኩረት ይሻሉ፡፡ ይህም የሚረጋገጠው በእቅድ ጊዜ በሚደረጉ ጥልቅ ግምገማዎች ነው፡፡
በታሪክና ባህል ከአለም ዋነኛዋ ሀገር የነበረችው ሀገራችን በዕድገትና በስልጣኔ ግን እስካሁን በዝግመት ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህም ዘመን የሶስተኛ ዓለም ሀገር ተብለን የምነጠራ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ (1990ዎቹ እ.አ.አ) አዳጊ ሀገር የሚል የማፅናኛ አይነት ስም ተለጥፎልናል፡፡
ይህ የሆነበት ምክንያት ለግምት የሚያዳግት ቢሆንም፤ ብዙዎች መረጃ እያጣቀሱና እየተነተኑ የየራቸውን ሀሳብ ያቀረቡበት ጉዳይ ስለሆነ ወደዚ መግባቱ ለጊዜው አስፈላጊ አይደለም፡፡ አንዱና ዋነኛው ችግር ግን ባለሙያነት የመጥፋቱና ስሜቱም  የመድከሙ ጉዳይ ሲሆን በዚህ ፅሁፍ ለማየት የተመረጠውም ይኸው ጉዳይ ነው፡፡ በዘመናችን ካለመው የጋዜጠኝነት ስራ ክዋኔ አንፃር እንደሚከተለው ታይቷል፡፡
ባለሙያ ማለት በቀላሉ ሙያን ገንዘቡ ያደረገ ማለት ነው፡፡ ሙያን ነጥለን ወስደን ስናይ ደግሞ ተግባርን በመለየት በመተንተን አቅዶ በተለያዩ መለኪዎች ውጤታማ የመሆን ስራን ያመለክታል፡፡ የስራ ዘርፍ ተመራማሪዎች የሙያተኛን ውጤታማነት በሶስት መለኪያዎች ይለኩታል፡፡ እነዚህም ጥራት፣ ብዛትና ጊዜ ናቸው፡፡ በመሆኑም የዘመናችን የጋዜጠኝነት ተግባር እንደ ስራ ሲታይ ጋዜጠኛው እንደባለሙያ ሲለካ ምን ይመስላል? በተለይተግዳሮቱስ ምንድን ነው?
በዘመናችን ያለ ጋዜጠኝነት ተግዳሮቶች መገለጫ ከሆኑት ተግባራት መካከል በዕለት ደራሽ ስራ መጠመድ፣ መረጃ ማግኘትን የስራው መጀመሪያና መጨረሻ አድርጎ መውሰድ፣ በጊዜ ሂደትና በጠንካራ ስነምግባር በሙያው የሚያድግ ባለሙያ እንደሚኖር መዘንጋትና ከግል አቅምና አቋም የዘለለ እይታ መገደብ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ከዚህ በመቀጠል እነዚህ አስተሳሰቦች እንዴት በሀገራችን የጋዜጠኝነት መህዳር ውስጥ ተግባራዊነታቸው እየሰፋ እንደመጣና ውጤታማነትን እየፈተኑ እንደሆነ እንመልከት፡፡
በእለት ደራሽ ስራ መጠመድ
ጋዜጠኛው የመስሪያ ቤት አደረጃጀት ሰለባ የሆነበት የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሀን ዘርፍ ዜናም ይሁን ዝግጅት በስምሪት የተባለ በሚመስል ተግባር እንደተጠመዱ ያመላክታል፡፡ በመሆኑም እቅድ ለይስሙላና ለስብሰበ ማጣፈጫ ከመወራቱ የዘለለ በመገናኛ ብዙሃን ተግባር የሰማይ ያህል የራቀ እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡
አሳሳቢው ጉዳይ ይህ ባህል ሆኖ በጀማሪ ባለሞያዎች ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተፅዕኖ ነው፡፡ ባለሞያዎች የጋዜጠኝነት ሞያ የዕለት ደራሽ ስራ የወጠረው ተግባር ሆኖ የዕቅድና የክትትል ዜናና ዘገባዎች ከጋዜጠኝነት ድርሳን እንዳይፋቁ የሚሰጋበት ዘመን ላይ እንደሆንን ብዙዎች ይነሳሉ፡፡
በድንገት ደራሽ ስራ መጠመድ የስራ መጀመሪያና መጨረሻ የሆነላቸው ጋዜጠኞች የዚህን ትግበራ ትሩፋቶች ከገፀ በረከትና ንዋይ ጥቅም አንስቶ ብዙ አውሪ ትንሽ ስሪ እንዳደረጋቸው ለማወቅ ከላይ የተጠቀሱትን መለኪያዎች በጥቂት ሞያተኞች ላይ በመተግበር ማየት ይቻላል፡፡
የስራን ክብደትና ቅለት የመለኪየው የሚያመጣው ውጤትና የሚፈጥረው ተፅዕኖ መሆኑ ቀርቶ ጋዜጠኛው ለጉዳዩ ጥንቅር የወሰደበት ጊዜና የጉልበት (በእንቅስቃሴና በማሰብ) መሆን መጀመሩ ከቀን ተቀን እንቅስቃያችን ማየት ጀምረናል፡፡
የእለት ደራሽ ስራ የፈጠራቸው ዕለት ደራሽ ጋዜጠኞች ተስፋና እርግማን በራሳቸውና በአስተማሪ አለቆቻቸው እጅ ነው፡፡ ቀደሞ የነቃና ተስፋውን የመረጠ ባለሙያ ቢኖር መጀመሪያ ማድረግ ያለበት ከዚህ አሰራር የሚወጣበትን ዕቅድ ለራሱና ለባልደረባው መስራት ነው፡፡
መረጃ ማግኘትን የሰራው መጀመሪያና መጨረሻ አድርጎ መውሰድ
በዘመናችን የማህበራዊ መገናኛ ብዙኃን ይህንን ጉዳይ ፉርሽ ያደረጉት ቢመስልም ጋዜጠኛው አሁንም የዚህ ተግባር / አስተሳሰብ ተጎጂ ነው፡፡ብዙዎች ራሳቸውን ለመከላከል የማህበራዊ መገናኛ ብዙኃንን ተአማኒነትን እያብጠለጠሉ  መረጃቸው ያልተጣራና ሙያዊ ስነምግባር የጎደለው ነው እያሉ ቢያነሱም፤ ከእነሱ የበለጡ ብዙዎች ደግሞ ጭራሽ እነዚህኑ የመረጃቸው ምንጭ ሲያደርጓቸው ይስተዋላሉ፡፡
የዘመናችን ጋዜጠኝነት ሰበር ዜና ማቅረብ የቀደመ ምን ብላ ….. አይነት ጨዋታ አድርጎታል ፡፡ የዚህ ጨዋታ ተጎጂ ደግሞ ጋዜጠኛው ራሱ ነው፡፡
በእውነት መረጃ ማግኘት ብቻ የጋዜጠኝነት ስራ መጀመሪያውና መጨረሻው ይሆን?  አንድ የእንግሊዝናኛ አባባል አዘውትሬ በትምህርትና ስራ ላይ እጠቀማለሁ “የተፃፈ ሁሉ ሊጠየቅ እንጂ እንዲሁ ሊቀበሉት አይገባም” መረጃ ያገኘ ጋዜጠኛ ሁሉ ባለሙያ የሆነ እየመሰለው ለሞያውና ለራሱ ሃፍረት እየሸመተ ያለባቸው ተግባራት ከግዜ ወደ ግዜ እየተበራከቱ መጥተዋል ፡፡
ድህረ ገፅ ላይ ዜና ወይም ሃተታ ለጥፎ መልሶ ማንሳት፤ ያልተሟላ መረጃ አትሞ ማስተባበያ ለማውጣት መራወጥ፤ የማይወክል ጉዳይ አስተላልፎ የይቅርታ መግለጫ ለማንጋጋት መጣር የዘመናችን ጋዜጠኞች መገለጫ ከሆኑ ውለው አድረዋል፡፡
አንድ ጋዜጠኛ መረጃ ማግኘቱ መጀመሪያው ቢሆንም መረጃው ለታዳሚ የሚኖረውን ፋይዳ መመርመር ከቻለ ዕሴት ጨመረበት ፤ ከዚያም አልፎ አቀራረቡን አወቀበት ፡፡ ይህም ባለሞያ የሚያሰኘው ተግባር ይሆናል ፡፡ በቅርቡ በአንድ መገናኛ ብዙኃን የአንድ አካባቢ የአየር ሁኔታ ዘገባ ሲሰራ የቦታው ከፍተኛ የሙቀት መጠን 80 ዲግሪ ሴልሽየስ ነው ብሎ ያቀረበ ጋዜጠኛ አስታውሳለው፡፡
ይህ መሰረታዊ እውቀትን የሚፈትን ዘገባ የጋዜጠኛው የ"መረጃ መጀመሪያና መጨረሻ" ጉዳዩ የሰረፀበትን ደረጃ አመላካች ሲሆን አንድምታው ግልፅ ነው፡፡ መረጃ ለማግኘት መፈልፈል መበርበር የጋዜጠኛ ስራ ነው ፡፡ መመርመር መተንተንና ማበጠር ይከተላል ፡፡ በመጨረሻ ለታዳሚ እንደሚጠቅም ማቅረብ ይሰልሳል፡፡
ይህ የመሰረታዊ የጋዜጠኝነት ተግባር ሀሁ መሆን ሲገባው በዕቅድ እንኳ ሊሰራ ያልቻለ ከፍተኛ ደረጃ ተግዳሮት ሆኖ በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ድባብ ላይ ይታያል፡፡
በጊዜ ሂደትና ጠንካራ ስነምግባር በሙያው ያለማደግ
የመገናኛ ብዙኃን ከሌሎች የሙያ ዘርፎች የተቀዱ የስራ መደቦችና እርከኖች ሲጠቀሙ ይስተዋላል፡፡ ከጀማሪ ዘጋቢ እስከ ዋና አዘጋጅ ያሉ ስያሜዎችም የብዙዎች የደብዳቤ ሲያልፍም የመታወቂያ ወረቀት መገለጫዎች ሆነዋል፡፡ ይህ በራሱ ችግር ባይኖረውም በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ግን ሁሉም ተቀላቅሎ አንድ ሆኗል ፡፡ ይህንንም ያመጣው  “ጋዜጠኛ” የሚለው የውል ስም ይመስለኛል፡፡
የጋዜጠኝነትና የተግባቦት ትምህርት ቤት በኢትዮጵያ ከአጫጭር ስልጠናዎች ደረጃ ተነስቶ እስከ ሁለተኛ ዲግሪ የሚሰራበት የትምህርት ዘርፍ ሆኗል የቀደሙት የመገናኛ ብዙኃን ማሰልጠኛ ተቋማትና ማሳያዎች ናቸው፡፡ዋናው ጉዳይ እነዚህ ተቋማት ባለሞያ ፈጥረዋልን? የሚለው ነው፡፡ ከሌሎች ሞያዎች ጋር ማነፃፀር የዚህ ፅሁፍ አላማ ስላልሆነ ወደዛ አልገባም፡፡
ነገር ግን ጋዜጠኝነት በግዜ ሂደትና በጠንካራ ስነምግባር በሙያ ልህቀት የሚታይበት ዘርፍ መሆኑ አጠራጣሪ እንደሆነባቸው ብዙዎች ይናገራሉ፡፡ ሙያ ከሚከፈል ተራ የስምሪት ይበልጣል ፡፡ ሞያ ወጣኒነት(ጀማሪነት) አዳጊነትና ብቁነት የሚታይበት የስብዕናና የአመለካከት መገለጫ ነው፡፡
ሙያ በዕቅድ ተሰርቶ የሚለወጡበትና የሚበቁበት ልዩ ፀጋ ነው፡፡ ሙያ መጨረሻ ለሌለው የእውቀት አለም ዜግነት ማግኛ መለያ ነው፡፡ በአገራችን ጋዜጠኝነት በአንድ ጀንበር ተንታኝ የሚኮንበት በሚቀጥለው ቀን መፍትሔ አመላካች ሊቅ የሚኮነንበት በሶስተኛ ቀን ያላየነው የለም የሚባልበት አሳዛኝ ዘርፍ ሆኗል ብለው ብዙዎች ያማርራሉ፡፡
ጋዜጠኝነት በታቀደና በተመረመረ ስራ የሚያድጉበትና በስብዕና የሚበለፅጉበት አልፈውም ለታዳሚ እሴት የሚሆኑበት ምዕራፍ ሊዘጋ አንድ እሁድ ቀረው ብለው ያዝናሉ ይቆጫሉ፡፡ በመሆኑም ጋዜጠኝነት በግዜ ሂደትና በጠንካራ ሞያዊ ስነምግባር ለማደግ የማይተጋበት ዘርፍ ለምን ሆነ ብለው ቢጠይቁ መልሱ ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ ባለዕዳ አይቀበለውም ይመስለኛል፡፡
በዕቅድ መመራትና በውጤት መለካት ከጋዜጠኝነት መንደር ኮብልለዋል፡፡ ይኽውም ለአቋራጭ መንገድ ተጠቃሚዎች በሩን በሰፊው ከፍቷል፡፡ ብዙዎች የባለስልጣናት ረዣዥም እጆችና የፖለቲካ ስርዓት ተፅዕኖዎችን በመጥቀስ ችግሩን በሌሎች ሊያላኩ ቢሞክሩም በራሳቸው መከራከሪያ ነጥብ ራሳቸውን ይጠልፋሉ፡፡ ባለቤቱ ያቀለለውን እንዳልን ከላይ!!
ከግል አቅምና አቋም ያልዘለለ ዕይታ
ዘመኑ ለጋዜጠኞች ዶሮ ብታልም ጥሬዋን ነው የሆነባቸው ይመስለኛል፡፡ ዕውቀትን በራሳቸው ትንሽ ቁና የሚሰፍሩ፣ መረጃን በራሳቸው የዕይታ አድማስ ውስጥ የሚፈልጉና፣ ጥበብን በራሳቸው የዕውቀት አድማስ ልክ ብቻ የሚተነትኑ ጋዜጠኞች በዝተዋል ብቻ አይገልፀውም፡፡ በእርግጥ አንድ እውነታ አለ አንድ ስራ መጀመሪያ ሰሪውን ካላረካ ሌላውን ያረካል ለማለት ይከብዳል፡፡
ነገር ግን ሰሪውና ስራው ማንና ምን ናቸው? የሚለውን እዚህ ጋር ማጤን ያስፈልጋል፡፡ በአንድ አጋጣሚ አንድ ጋዜጠኛ ጣቢያው የሰራው ልዩ ፕሮግራም ከሌላው የተሻለ እንደሆነ ሲገልፅልኝ የተየኩት አንድ ጥያቄ ብቻ ነበር እርሱም “በማን መለኪያ” የሚል ነበር በሰሩት ስራ መርካት ችግር የለበትም ችግሩ የሚጀምረው የሰሩት ስራ ለሌሎች ስራዎች ማንፀሪያነት የደረሰ የመጨረሻ ተግባር ነው ብለው የወሰዱት ግዜ ነው፡፡ በመሆኑም ጋዜጠኞችና መገናኛ ብዙኃን በራሳቸው አቅም ልክ ታዳሚን መገመት ሲጀምሩ የመጨረሻው መጀመሪያ ይሆናል፡፡
የዘመናችን ጋዜጠኞች ሌላው ችግር የግል አቋምን የአብዛኛው አቋም አድርጎ መሳል ነው፡፡ ይህ ነገር ካለማስተዋል ከሆነ በምክርና በትችት ሊስተካከል ይችላል ነገር ግን ሆን ተብሎ የተሰራ ከሆነ መመለሻው አደገኛ ማጣፊያው አጭር ይሆናል፡፡ የዚህ ፅሁፍ አንባቢም ይህ ትንተና በአቅምና በአቋም ላይ ተመስርቶ በበጎ ለበጎ የተዘጋጀ እንደሆነ ይረዳው ዘንድ እለምናለው፡፡
የጋዜጠኞች ከግል አቅምና አቋም ያልዘለለ ዕይታ የተለያዩ ምክንያቶች ሊኖሩት ይችላሉ፡፡ ከላይ እንደተገለፀው አንዱና ዋነኛው መረጃ ማግኘትን የመጀመሪያና የመጨረሻው አድርጎ መውሰድ ነው፡፡ በመሆኑም መረጃን ለመጠየቅና ልምድ ያለመኖር የአቅም ውስንነትን ያመጣል፡፡
ሌላው ምክንያት በግዜ ሂደትና በጠንካራ ስነምግባር በሙያው ያለማደግ ነው፡፡ በመሆኑም ጋዜጠኞች ጉዳዮችና የመመርመርና የመተንተን ችሎታና ፍላጎት ሲከዳቸው አቋም አራማጆች ሆነው ያርፉታል፡፡  ዘወትር እንደሚነሳው ሁነኛ የቃለመጠይቅ ጥያቄ ማዘጋጀት እየተሳናቸው ጥያቄዎቻቸው "ምን ይላሉ?" እና "ምን ይሰማዎታል?" የሚል ይሆናል፡፡
አንዱ ጋዜጠኛ አንድ እንግዳውን ምን ይሰማዎታል ብሎ ቢጠይቅ ችብግዳው "ንዴት" ብሎ መለሰለት መልሱ ያልተዛመደለት ጋዜጠኛ "በምን?" ቢለው "በአንተ ተራ ጥያቄ" ብሎት ሄደ የሚል ቀልድ ብዙዎቻችን የሰማን ይመስለኛል፡፡
ምን ይሻላል?
ጋዜጠኝነት በእለት ደራሽ ስራ ብቻ የመጠመድ አባዜ አይደለም፡፡ ነገር ግን ጋዜጠኝነት በጊዜ ሂደትና በጠንካራ ስነ ምግባር በሙያ የሚያድጉበት፣ መረጃ ማግኘት የስራው መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ ያልሆነበት፤ ይልቁንም ከግል አቅምና አቋም የዘለለ ሰፊ ሞያዊ ዕይታን የሚፈልግ መመርመርን የሚሻና አዘውትሮ መጠየቅን የሚያስገድድ ተግባር ነው፡፡
በመሆኑም ይህ ጉዳይ የማይሆንበት ሁሉ አቋርጦ ቢመለስ፤ ለመቆየት የወሰነ ካለ ግን የስራውን ባህርይ ተገንዝቦ ራሱን ማትጋት ይገባዋል፡፡ የስራ መሪዎች ፤ የትምህርትና የስልጠና ተቋማት በዘርፉ የቆዩ ባለመያዎች ራሳቸውን የሚፈትኑበት ጊዜ ቢያልፍም "ከመቅረት መዘግየት ይሻላል" እንዲሉ በቀረው ጊዜ ሁኔታዎችን ለማስተካከል ቢሰራ መልካም ነው፡፡
ምን ይሰራ?          
"እዳው ገብስ ነው" ይባላል ችግሩ በሌሎቹ ዘርፎችም እንዳለ ሁሉ የሙያውን አላማ ጠንቅቆ ማወቅ የብዙሃን መገናኛዎች ራዕይና አላማ አበጥሮ መለየትና ከሚሰሩት ስራ ሁሉ ውጤቶችን መጠበቅ ናቸው፡፡ አንደኛ ራስን መለወጥ ሁለተኛ ሌላውን /ታዳሚን ለመለወጥ ማቀድ፡፡
ይህስ ከሆነ በኋላ ሁሉም ነገር መልካም ይሆናል ማለት ነው? ውጤታማነት ይጎላል ማለት ነው? መልሱ "ይሆን ይሆናል" ይመስለኛል ፡፡ በእርግጠኝነት የሚታወቀው ደርሰን ስናየው ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ሄደዋላ!!